Translation is not possible.

ታሪክ እራሱን እየደገመ ይመስላል

ቁጥራቸው ዘጠና ዘጠኝ ነበር። መሪያቸው ዐብዱላህ አት-ቱል ይሰኛል። እየሩሳሌምን ትተው ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲመለሱ፣ ከሞቀው ፍራሽ ጎናቸውን እንዲያሳርፉ በእንግሊዝ ጦር ፈቃድ ተሰጣቸው።

እነርሱ ግን ቁድስን ለመጠበቅ የጠላትን ጦር ፊት ለፊት ለመጋፈጥ ወሰኑ። ለመስጂደል አቅሳ እየተከላከሉ ጌታቸውን ለመገናኘት ፈለጉ። ሁሉም እስከ መጨረሻው የደም ጠብታ ጸንተው ኢየሩሳሌም እየጠበቁ ሸሂድ ሆነው ከአጥሯ ወደቁ።

እኚህ ስድስቱ የዮርዳኖስ ጀግኖች ሸሂድ ከመሆናቸው ከአንድ ቀን በፊት ድንኳናቸው በር ላይ በፈገግታ የተነሱት ምስል ነው። አላህ ቀብራቸውን ኑር ማረፊያቸውንም ጀነተል ፊርደውስ ያድርግላቸው።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group