Translation is not possible.

በዚህ ሰሞን መደሰት እንደክህደት ይሰማን ጀምሯል። ከአልጋችን መተኛትም ክህደት መስሎ ይታየናል። መሳቅ እንኳ ይከብደናል፣ እነሱ አዝነው ሳለ የኛ መሳቅ ትልቅ ክህደት ሆኖብናል።

በዚህ ሰሞን በምንም ጉዳይ መደሰት በእነሱ ሀዘን ላይ ክህደት እንደመፈፀም ይሰማናል። ምንም ማድረግ ካለመቻላችን የተነሳ በህይወት መኖራችን ያሳፍረናል። ‹‹እንዴት አደርክ?›› ለሚለው ጥያቄ ምላሽ አጥተናል።

አዎን! እምነት ያስተሳሰረን ወገኖቻችን ጎድለውብናል። ኢላህ ቃልህን ምትሞላ ነህ'ና ቃል የገባህልንን ድል አሳየን!

Follow

Send as a message
Share on my page
Share in the group