Translation is not possible.

አይኑ የታመመ ብርሃን አይመቸውምና...

አላህ (ለዓለም እዝነት አድርገን እንጂ አላክንህም) እና (አንተን የሚጠላ ዘሩ የተቆረጣ፤ ከመልካም ነገር በሙሉ የተራቆተ ነው) ያለላቸው ነቢይ ላይ

ሰለዋት አብዙ።

اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ بِعَدَدِ مَنْ صَلَّى عَلَيْهِ، وَصَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ بِعَدَدٍ مَنْ لَمْ يُصَلِّ عَلَيْهِ.

አይኑ የታመመ ብርሃን አይመቸውምና የዲናቸው ብርሃን አለምን ማጥለቅለቁ ሳይመቸው ቀርቶ ልቡ ተጣቦ ስማቸውን በክፉ ያነሳን በሙሉ "በቁጭትህ ሙት። የጸሐይን ብርሃን መጋረድ ከማትችለው በላይ የዲናቸውን ብርሃን መጋረድና ማስቆም አትችልም" በሉት።

ጥላቻ ያሳወረው በሙሉ ቁጭት እንዲገድለውም በሁሉም ቦታና ሁኔታ ላይ የጠላቸውን ነቢይ ሱና በመተግበር ምድርን በለፉለት ዲን ብርሃን እናሸብርቃት።

ዛዱል-መዓድ

اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ بِعَدَدِ مَنْ صَلَّى عَلَيْهِ، وَصَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ بِعَدَدٍ مَنْ لَمْ يُصَلِّ عَلَيْهِ.

Send as a message
Share on my page
Share in the group