UMMA TOKEN INVESTOR

Tentang saya

- አንዲትም አንቀፅ ብትሆን ከእኔ አድርሱ - ረሱል ﷺ

Terjemahan tidak mungkin.

For best Islamic twit follow me

image
Hantar sebagai mesej
Kongsi di halaman saya
Kongsi dalam kumpulan
Terjemahan tidak mungkin.

ጋዛ ውስጥ በ1965 (እአአ) የተወለደው ሞሐመድ ዳይፍ አል-ማስሪ በቅጽል ስሙ “አቡ-ኻሊድ” ወይም “አል-ዳይፍ” የሐማስ ወታደራዊ ክንፍ የሆነው የኢዝ አል-ቃሳም ብርጌድ መሪ ነው።

በፍልስጥኤማውያን ዘንድ “ዋነኛው አንቀሳቃሽ” በመባል የሚታወቅ ሲሆን፣ እስራኤላውያን ደግሞ “የሞት መልዕክተኛ” ወይም “ባለዘጠኝ ነፍሱ ተዋጊ” በሚል ይጠራል።

ሞሐመድ ዳይፍ ጋዛ ውስጥ ከሚገኘው እስላማዊ ዩኒቨርስቲ ባዮሎጂ አጥንቶ በዲግሪ የተመረቀ ሲሆን፣ በዩኒቨርስቲ ቆይታው ለትወና እና ለቲያትር ባለው ፍቅር እንዲሁም የኪነ ጥበብ ቡድን በማቋቋሙ ይታወቃል።

ዳይፍ ሐማስ መመሥረቱ ሲገለጽ ቡድኑን የተቀላቀለው በሙሉ ልብ አልነበረም። በ1989 (እአአ) ለሐማስ ወታደራዊ ቡድን ይሠራል ተብሎ በእስራኤል ባለሥልጣናት ከተያዘ በኋላ ያለፍርድ ቤት ውሳኔ ለ16 ወራት ታስሮ ነበር።

በእስር ላይ በቆየበት ጊዜም ዳይፍ ከዛካሪያ አል-ሾርባጊ እና ከሳላህ ሺሃዲህ ጋር በመሆን ከሐማስ የተለየ የእስራኤል ወታደሮችን የሚማርክ ቡድን ለመመሥረት ተስማማ። ይህ እንስቃሴ ነው እንግዲህ ጎልብቶ አል-ቃሳም ብርጌድ ለመሆን የቻለው።

ዳይፍ ከእስር ከተፈታ በኋላ የኢዝ አል-ቃሳም ብርጌድ ወታደራዊ ቅርጽ በመያዝ መንቀሳቀስ ጀመረ፣ ዳይፍም ከሌሎች የቃሳም መሪዎች ጋር በመሆን የቡድኑ ቀዳሚ መሥራች ለመሆን ቻለ። የደይፍ የሀማስ ተዋጊዎች ከጋዛ ተነስተው ወደ እስራኤል እንዲገቡ የሚያስችላቸውን የመሬት ውስጥ መተላለፊያ ዋሻን የቀየሰው እና ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ሮኬቶችን በአንድ ጊዜ የመተኮስ ሃሳብን ካራመዱት መካከል አንዱ ነው።

ከሁሉም በላይ በእስራኤል ከሚቀርቡበት ከባባድ ክሶች መካከል የሐማስ ቦምቦችን ይሰራ የነበረውን የያህያ አያሽ ግድያን ለመበቀል እንደ አውሮፓውያኑ 1996 መጀመሪያ ላይ 50 እስራኤላውያን የተገደሉባቸውን የአውቶብስ የቦምብ ጥቃቶች፣ እንዲሁም በ1990ዎቹ አጋማሽ ተማርከው የተገደሉ ሦስት እስራኤላውያን ጉዳይ ይጠቀሳሉ።

እስራኤል ዳይፍን በ2000 ላይ ይዛ አስራው የነበረ ቢሆንም፣ ሁለተኛው የፍልስጥኤማውያን አመጽ ሲቀሰቀስ ለማምለጥ ችሏል። ከዚያ በኋላም የት እንዳለ አይታወቅም።

አስካሁን የሚታወቁ የዳይፍ ሦስት ፎቶዎች አሉ። አንደኛው በጣም ያረጀ፣ ሁለተኛው ጭምብል አድርጎ እና ሦስተኛው ጥላውን የሚያሳዩ ናቸው።

ዳይፍ በጣም አደገኛ የሚባል የመግደል ሙከራ የተደረገበት በ2002 (እአአ) ነበር። በጥቃቱ ዳይፍ ተዓምር በሚባል ሁኔታ ቢተርፍም አንድ ዐይኑን አጥቷል። አስራኤል ግን በጥቃቱ በተጨማሪ አንድ እጁን እና እግሩን ማታቱን እንዲሁም በተደጋጋሚ በተፈጸሙበት የግድያ ሙከራዎች ምክንያት የመናገር ችግር ገጥሞታል ትላለች።

በአውሮፓውያኑ 2014 የእስራኤል ሠራዊት ለ50 ቀናት የቆየ ጥቃትን በጋዛ ሰርጥ ላይ ባካሄደበት ጊዜ ዳይፍን ለመግደል ሳይችል ቢቀርም፣ ሚስቱን እና ሁለት ልጆቹን ገድሏል።

የሐማሱ ወታደራዊ ክንፍ መሪ ዳይፍ የሚለውን ስም የወሰደው “እንግዳ” ከሚለው የአረብኛ ቃል ነው። ምክንያቱም የእስራኤልን ግድያ ለማምለጥ አንድ ቦታ ላይ ለረጅም ጊዜ ስለማይቆይ እና በየምሽቱ ለማደሪያነት የሚጠቀምብትን ስፍራ ስለሚቀያይር ነው።

ፈጣን እና ተአማኒ ለሆነ መረጃ #follow ያድርጉ

image
Hantar sebagai mesej
Kongsi di halaman saya
Kongsi dalam kumpulan
Terjemahan tidak mungkin.

🌸 አል ነጃሺ አላህ ይውደድለትና እንዲህ አለ፡-

የሀበሻ፣ የካህናት እና የመነኮሳት ማህበረሰብ ሆይ፦ መሐመድ የአላህ መልእክተኛ (صلى الله عليه وسلم) መሆናቸውን እና በወንጌል ውስጥም ተጠቅሰው የምናገኛቸው እሳቸው መሆናቸውን እመሰክራለሁ።የመርየም ልጅ ዒሳም ብስራትም ናቸው። በአላህ እምላለሁ ይሄ ያለሁበት ንግሥና ባይዘኝ ኖሮ ጫማውን ተሽክሜ የማሳጥበው እኔ እሆንለት ዘንድ ወደርሱ እመጣ ነበር።

📚سنن سعيد بن منصور (٢٤٨٦)📚

Hantar sebagai mesej
Kongsi di halaman saya
Kongsi dalam kumpulan
Terjemahan tidak mungkin.

ሃማስ ለእስራኤል የምድር ጦር ወረራ ምለሽ ለመስጠት ዝግጁ ነኝ አለ

ሃማስ እስራኤል በጋዛ ለምታካሂደው የምድር ወረራ ተገቢውን ምለሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።

የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይ ዛሬ ማምሻውን በሰጠት መግለጫ፤ የምድር ኃይላችን በጋዛ የሚያደርገውን ዘመቻ ከዛሬ ምሽት ጀምሮ አስፋፍቶ ያካሂዳል ብለዋል።

የህንን ተከትሎ ሃማስ እስራኤልወረራ ከፈጸመች ዝግጁ ነኝ ማለቱን አስታውቋል ።

አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ

image
Hantar sebagai mesej
Kongsi di halaman saya
Kongsi dalam kumpulan
Terjemahan tidak mungkin.

ጽዮናዊነት ምንድን ነው?

ጽዮናዊነት በአውሮፓ በ19ኛው ክፍለ ዘመን የተጀመረ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ነው።

ፍልስጥኤም በምትባለውም ምድር የአይሁድ አገርን መመሥረት ዋነኛ ግቡ ነው።

ይህ እንቅስቃሴ የአይሁዳውያን የጥንት ርስት ናት የሚሏትን የአይሁዳውን አገር የሆነች እስራኤል ፍልስጥኤም ተብሎ በሚታወቀው መሬት የመመሥረት ፍላጎት የነበረው ነው።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትም ፍልስጥኤም ለሁለት ተከፍላ የአይሁዶች እና የአረቦች የተናጠል አገራት አንዲመሠረቱ ሃሳብ አቀረበ።

በአውሮፓውያኑ 1948ም እስራኤል በመካከለኛው ምሥራቅ ውስጥ በአገርነት መመሥረቷ ታወጀ።

በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ፍልስጥኤማውያን ከቀያቸው እና ከቤታቸው ተፈናቀሉ። ከዚያም በኋላ በ1967 (እአአ) የተደረገውን የስድስቱን ቀን ጦርነት ተከትሎ የፍልስጥኤም ግዛቶች የሚባሉትን ዌስት ባንክን እና ምሥራቅ ኢየሩሳሌምን እስራኤል በኃይል ተቆጣጥራ ትገኛለች።

ባለፉት አምስት አስርት ዓመታትም በነዚህ ግዛቶች የአይሁዶች የሰፈራ መንደሮችን አቋቁማለች። 700 ሺህ የሚቆጠሩ አይሁዳውያን በእነዚህ ስፍራዎች አስፍራለች።

የተባበሩት መንግሥታትን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማት እስራኤል በቁጥጥሯ ስር ባሉ ግዛቶች የሰፈራ መንደሮችን ማቋቋሟ ዓለም አቀፍ ሕግን የሚጻረር እና ሕገወጥ ነው ሲሉ ይጠሩታል።

የእስራኤል መንግሥት ምሥረታ በፍልስጥኤም የሚኖሩ አረቦችን መብት የነፈገ መሆኑን በመጥቀስ ፍልስጥኤማውያን እንዲሁም ሌሎች አረቦች ይቃወሙታል።

የጽዮናዊነትን እንቅስቃሴ የሚያቀነቅኑ አካላት እስራኤል እንደ አይሁድ ግዛትነቷ ጥበቃ ሊደረግላት እንዲሁም ልትስፋፋ ይገባል ብለው ያምናሉ።

አንዳንድ ጽዮናውያን እስራኤል ካላት ግዛት በተጨማሪ ሌሎች ግዛቶችንም የመቆጣጠር መብት አላት ብለው የሚከራከሩ ሲሆን፣ ሌሎች በዚህ ሃሳብ አይስማሙም።

አብዛኛው አይሁዳውያን ጽዮናውያን ቢሆኑም፣ ጥቂቶች በፖለቲካዊ እና በሃይማኖታዊ ምክንያቶች ጽንሰ ሃሳቡን ይቃወማሉ።

ፈጣን እና ተአማኒ ለሆነ መረጃ #follow ያድርጉኝ

Zulbejadein

image
Hantar sebagai mesej
Kongsi di halaman saya
Kongsi dalam kumpulan