UMMA TOKEN INVESTOR

About me

Islam is the way of truth life ❤

Hanan Tejineh shared a
Translation is not possible.

#ሳውዲ_የታሰረችው ከ4 ወር በሗላ የተጠየቀችውን ብር ካልከፈለች #ሞቷን_አስቀድሞ_የተነገራት #የቡታጅራ ተወላጅ የሆነችው #የለይላ_ኑርሰቦ ጉዳይ #የሁሉም ሰው ጉዳይ ስለሆነ #ልንደርስላት ይገባል፡፡

###################

የለይላ ኑርሰቦ ጉዳይ #በቤተሰቦቿ :#በበጎ_አድራጎት_ማህበሮች #በእድሮች #በነጋዴዎች #በአርሶ_አደሮች #በመንግስት_ሰራተኞች #በወረዳ #በከተማ #በዞን #በኢትዮ_ሳውዲ ብቻ የሚፈታ ችግር አይደለም የእሷ ጉዳይ #ሰው_ለሆነ ሁሉ ጉዳይ ነው ቢሆንም እኛ #ያልጀመርነው ችላ ያልነው ጉዳይ መቼም #ኢትዮ_ሳውዲ_ኢምባሲ ትኩረት ይሰጠዋል ብሎ መጠበቅ ከባድ ነው፡፡

እውነት ለመናገር እቺ ልጅ #እህትክ_እህትሽ ብትሆን በዚህ ልክ አትዘናጋም ነበር? እባካችሁ ነግ በኔ ነው #እንተጋገዝ_አንጨካከን ለበጎ ተግባር ማንንም መጠበቅ አያስፈልገውም፡፡

#የቡታጅራ ህዝብ ደግሞ #በጎነት ወትሮም #ልማዱ ነው አሁንም በእህቱ #የሚጨክን አንጀት ያለው ሰው የለም #የመጠባበቅ ጉዳይ ሆኖበት ይመስለኛል፡፡

######ጉዳዩ እንዲህ ነው####

11 ዓመት እስር ቤት ያለች እህት 😭

ለይላ ኑርሰቦ ትባላለች ። የቡታጅራ ልጅ ናት ። ለይላን እናት ና አባቷም መሬት ሽጠው በ2005 ነበር ወደ ሳውዲ የላኳት ። ቤተሰቤን እለውጣለሁ ብላ ሳውዲ ከሄደች 11 ዓመት ሆናት ...

ነገር ግን

ሳኡዲ በመጣች በ5 ወሯ ሰውየው ሊደፍራት ሲታገል " ፈጣሪ የሚጠላው ነገር ነው ፣ ሀራም ነው " ብላ እሱን እማታለው ብላ ሳታቅ የአሰሪዋን ልጅ መታቻት ህፃኗ ከ 5 ወር በኃላ ሞተች 😪

የሳውዲ ህግ የገደለ ይገደል ነውና በለይላም የሞት ፍርድ ተፈረደባት 😪 በስተመጨረሻ የሳውዲ ቃዲዎች ጉዳዩን በጥልቀት እንደገና በማየት ፍርዱን በብር ቀየሩላት፡፡

ምክንያቱም

1ኛ ልጅቷን የገደለቻት አስባ አለመሆኑ(በስህተት መሆኑን)

2ኛ ልጅቷ የሞተችው ከመታችት ከ6 ወር በሗላ መሆኑን ከግንዛቤ በማስገባት ነው፡፡

እህታችንን ከእስር ቤት ለማውጣት 2 ሚሊዮን የሳውዲ ሪያል በኢትዮጵያ 60,000,000 ብር ተጠይቋል ይህንንም በአንድ ዓመት ውስጥ አስገቡ ተብሏል ።

ለቤተሰቡ ከኢምባሲ መረጃው የደረሰን ውሳኔው ከተወሰነ ሊጠናቀቅ 4 ወር ብቻ ሲቀረው ነው ይላሉ፡፡

ቤተሰቦቿ እያለቀሱ ነው

"ልጃችን ከሀገር ከወጣች 11 ዓመት ነው 11ኑንም ዓመት ታስራለች ፣ የሞት ፈርዶ ጠብቋታል ፣ 11 ዓመት ጠብቀን ትመጣለች ብለን ስንጠብቅ ልጃችንን ሊገድሉብን ነው 😪 የልጃችንን ዓይን ማየት እንፈልጋለን 😭 11 ዓመት እያለቀሰን ነው😭

እርዱን ፣ ልጃችንን አድኑልን

እኛን ለመለወጥ ነበር ሳውዲ የወጣችው 😪 " እያሉ ያለቅሳሉ

አባቷ ሲያለቅስ ያሳዝናል 😭

እናቷ ስታለቅስ ታሳዝናለች 😭

አሁን የምትገኘው ሳውዲ መነዝ እስር ቤት ላይ በስቃይ ነው

እህታችንን ከሞት ፍርድ ከስቅላት እናድናት 🤲

መርዳት ባትችሉ share በማድረግ የሚረዳትን ሰው ያፈላልጉ

እህታችንን ለመርዳት 1000571065065

image
image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Hanan Tejineh shared a
Translation is not possible.

መህዲ ማነው?

‹‹መህዲ›› በመጨረሻው ዘመን ከደጃልና ዒሳ መምጣት አስቀድሞ የሚነሳ ታላቅ ‹‹ኸሊፋ›› ነው። ‹‹መህዲ›› የማዕረግ ስሙ ሲሆን ‹‹ሁዳ›› ከሚለው ቃል የተገኘና ‹‹የተመራ ቅን ኸሊፋ›› ማለት ነው። መጠሪያ ሙሉ ስሙ ደግሞ ‹‹ሙሐመድ ኢብን አብዱላህ አል-መህዲ›› ነው።

ስለ መህዲ በቁርኣን የተነገረ ምንም ነገር አናገኝም። መረጃዎቹ በሙሉ ከሐዲስ የተገኙ ሲሆን ከሃያ በላይ የተረጋገጡ ዘገባዎች ይገኛሉ። ብዙ የሱንና ዑለማዎች ስለ መህዲ የፃፉ ሲሆን ቲርሚዚና አቡ-ዳውድ ራሱን የቻለ ምዕራፍ ሰጥተውታል።

ከሁሉም ታዋቂው ሐዲስ አቡ-ዳውድ የዘገቡት ሲሆን ነቢዩ (ዐሰወ) እንዲህ ብለዋል፡-

‹‹ትንሳኤ ሊቆም አንድ ቀን ቢቀረው እንኳን አላህ ከቤተሰቤ የሆነን፤ ስሙ ከእኔና ከአባቴ ጋር የሚመሳሰል መሪን ሳያስነሳና በበደል የተዋጠችውን ምድር በፍትህ ሳይሞላት አይተዋትም።››

(አቡ-ዳውድ 4282)

ከዚህ ሐዲስ እንደምንረዳው መህዲ የነቢዩ (ዐሰወ) ቤተሰብ ነው። ስሙም የነቢዩን (ዐሰወ) እና አባታቸውን የያዘ ሲሆን ‹‹ሙሐመድ ኢብን አብዱላህ›› ወይም ‹‹አህመድ ኢብን አብዱላህ›› ነው። የሚመጣውም ዓለም በዙልም በተዋጠችበት በመጨረሻው ዘመን ሲሆን የአላህን ቃል ከፍ በማድረግ ፍትህን ያነግሳል።

ኡሙ ሰላማ (ረዐ) እንደተናገረችው ነቢዩ (ዐሰወ) ‹‹መህዲ በፋጡማ በኩል የሚገኝ ቤተሰቤ ነው።›› ብለዋል። ኢብኑል ቀይም ይሄንን ሐዲስ ሲያብራሩ ‹‹መህዲ የሐሰን ዘር ሲሆን አል-ሐሰን ለሙስሊሙ አንድነት ሲሉ ኸሊፋነታቸውን አሳልፈው በመስጠታቸው ምክንያት አላህም በመጨረሻው ዘመን ከቤተሰባቸው ታላቅ ኸሊፋ በማስነሳት ክሷቸዋል።›› ሲሉ ፅፈዋል።

(አቡ-ዳወድ 11/373)

አቡ-ሰዓድ አልኩድሪ በዘገቡት ሐዲስ ነቢዩ (ዐሰወ) ስለ መህዲ ገፅታ ሲናገሩ ‹‹ቁመቱ ረጂም፣ ትከሻው ሰፊ፣ አፍንጫው አጠፍ ያለ ነው።›› ብለዋል።

(አቡ-ዳውድ 4265)

መህዲ የሚነሳበትን ቦታ በተመለከተ የተለያዩ ዘገባዎች አሉ። ከፊሎቹ ከሻም ከፊሉ ከኹራሳን ሌላው ደግሞ ከመዲና እንደሆነ ይናገራሉ። ኢብን ከሲር የሁሉንም ሐዲሶች ጥቅል ሀሳብ ሲያስቀምጡ ‹‹የሚነሳው ከምስራቅ ነው። ከዚያም ወደ መካ ይሄዳል። ሰዎችም በከዓባ ዙሪያ ቃልኪዳን ይገቡለታል።›› ብለዋል። እንዲሁም በሌላ መጽሐፋቸው ‹‹በሐዲስ በተጠቀሰው መሰረት ባንዲራው ጥቁር ነው።›› በማለት አብራርተዋል።

(አልቢዳያህ ወልኒያህ 19/63፤ አልፊታን ወልመላሂም 1/49)

ኢማም አህመድ እንደዘገቡት መህዲ መሪነት ሲመረጥ ፍላጎቱም ክህሎቱም አልነበረውም። እናም ‹‹አላህ በአንድ ሌሊት ይመራዋል።›› ብለዋል (ዐሰወ)። ኢብን ከሲር ሐዲሱን ሲያብራሩ፡- ‹‹ይህ ማለት አላህ ይረዳዋል፣ ከዚህ በፊት ያልነበረውን ችሎታም ይሰጠዋል ማለት ነው።›› ብለዋል።

(አህመድ 2/58/ አልፊታን ወልመላሂም 1/29)

መህዲ ኸሊፋነትን ከተረከበ በኋላ ሙስሊም አገራትን በአንድ በማፅናት በቀደመው ኢስላማዊ አስተዳደር ስር ያስገባቸዋል። ከዚያም በቡኻሪ እና ሙስሊም (2897) እንደተዘገበው ከሮማውያን ጋር የመጨረሻው ታላቁ ጦርነት ‹‹አል-መልሃማ አል-ኩብራ›› ይካሄዳል። ሙስሊሞችም ዳቢቅ ላይ ድል ደርጋሉ። ከዚህ በፊት ያልተከፈቱ አገራትንም ይከፍታሉ። ከዚያ በኋላ ሙስሊሞች በየትኛውም ኃይል አይሸነፉም። አላህ አማኞችን ከፍተኛ የሀብት መትረፍረፍ ይባርካቸዋል።

ሸይህ ዑመር ሱለይማን አል-አሽቀር ሐዲሱን መሰረት በማድረግ እንደተናገሩት ‹‹ይህ ጦርነት ከባድ ውድመትን ስለሚያስከትል ዓለም አሁን ካለችው ስልጣኔ ወደኋላ በመመለስ እንደ ጥንቱ በጦር በጋሻ በፈረስ መጠቀም ይጀምራሉ።›› ብለዋል።

(አል-ቂያማህ አስ-ሱግራ 275)

መህዲ ታላቅ ጦርነት አድርጎ ሙስሊሞችን የበላይ ቢያደርግም ጊዜው የቂያማህ ቀን መቃረቢያ በመሆኑ ከባባዶቹ ፊትናዎች ይከሰታሉ። ከእነዚህም መካከል ቀዳሚው የደጃል መነሳት ነው። እሱን ተከትለው የዕጁጅና መዕጁጆች ከጉድጓዳቸው ይወጣሉ። በዚህ ጊዜ አላህ ዒሳን (ዐሰ) ለእርዳታ ይልከዋል።

በሐዲስ እንደተጠቀሰው ዒሳ (ዐሰ) ወደ ምድር የሚወርደው በፈጅር ሰላት ወቅት ነው። ነቢዩ (ዐሰወ) ስናገሩ ‹‹መህዲ ዒሳን አሰግደን ይለዋል። ዒሳም እናንተ መሪዎች መሆናችሁ ከቂያማህ ምልክቱ ነውና አንተ አሰግደን ይለዋል። ዒሳም ከመህዲ ኋላ ተከትሎ ይሰግዳል።›› ብለዋል።

(ሙስሊም 225)

ከዚያ በኋላ ዒሳ ከሙስሊሞች ጋር በመሆን የዕጁጆችንና ደጃልን በመጋደል በአላህ ዕርዳታ ያጠፋቸዋል። ነቢዩ (ዐሰወ) እንደተናገሩት ‹‹ሙስሊሞች ለሰባት ዓመታት ያህል የየዕጁጆችን አጥንት ቀስትና ጋሻ ለማገዶነት ይጠቀሙበታል።

መህዲ በኸሊፋነት የሚቆይባቸው ዓመታት ‹‹ሰባት›› እንደሆኑ አብዛኛዎቹ የሐዲስ ምሁራን ይናገራሉ። ከእነሱ መካከል አንዱ የኢብኑ ማጃህ ሲሆኑ ነቢዩ (ዐሰወ) ‹‹መህዲ ሰባት አጭር ጊዜያትን ይቆያል።›› ማለታቸውን ዘግበዋል።

(ኢብን ማጃህ 4039)

አል-መህዲ እስኪመጣ ሙስሊሙ ጂሐድን በመተው መጠበቅ ይኖርበታል? ለሚለው ጥያቄ ሸይህ ሙሐመድ ሷሊህ አል-ሙነጂድ በፈትዋ ገፃቸው እንዲህ ብለዋል፡-

‹‹ከጂሐድ መዘንጋት ከከባባድ ወንጀሎች አንዱ ነው። አላህ ያዘዘው ሁሉም የራሱን ግዴታ እንዲሞላ ነው። መህዲ የራሱ ጂሐድ አለው። ይሄም ህዝብ የራሱን ጂሐድ ማድረግ ግዴታው ነው።

#አላህ በቁርኣኑ እንዲህ ይላል፡-

وَقَاتِلُوهُمْ حَتَّىٰ لَا تَكُونَ فِتْنَةٌ وَيَكُونَ الدِّينُ كُلُّهُ لِلَّهِ ۚ فَإِنِ انتَهَوْا فَإِنَّ اللَّهَ بِمَا يَعْمَلُونَ بَصِيرٌ

ሁከትም እስከማትገኝ ሃይማኖትም ሁሉ ለአላህ ብቻ እስከሚኾን ድረስ ተጋደሏቸው፡፡ ቢከለከሉም አላህ የሚሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነው፡፡

[ ሱረቱ አል-አንፋል - 39 ]

®ምንጭ"face book.ድ/ገጽ"

©ኮፒ ራይት"

#ዘላለም_ኗሪ_አላህ_ነው

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Hanan Tejineh Changed her profile picture
7 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

Free palestinians

Send as a message
Share on my page
Share in the group