Translation is not possible.
የኬንያ ፖሊስ የተቆራረጠ አስክሬን በቦርሳ ይዞ ሲጓዝ የነበረን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር አዋለ።
የ29 ዓመቱ ጆን ኪያማ ዋምቡያ አስክሬኑ የ19 ዓመት ሚስቱ እንደሆነ ተናግሯል። ፖሊስ በናይሮቢ ሁሩማ ግዛት ቅኝት ሲያደርግ ነው ግለሰቡን የያዘው።
ግለሰቡ ሕገ ወጥ ነገር እንደያዘ በመጠርጠር ፖሊስ አስቁሞት ቦርሳውን ሲፈትሽ የተቆራረጠ አስክሬን አግኝቷል።
የኬንያ ወንጀል ምርመራ "በጣም አስደንጋጭ ነበር" ሲል የገጠመውን ገልጿል።
ሴቶች ላይ የሚፈጸም ግድያ ከፍተኛ ከሆነባቸው አገሮች መካከል ኬንያ አንዷ ናት።
ግለሰቡ ላይ ፖሊስ ባደረገው ምርመራ ነው አስክሬኑ የባለቤቱ ጆይ ፍሪዳ ሙናኒ እንደሆነ የደረሰበት።
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group