2 years Translate
Translation is not possible.
- ወራሪዋ እስራኤል ደህንነቱ የተጠበቀ ቦታ ነው ያለችው፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ስደተኞች ጊዜያዊ ጎጇቸውን የቀለሱበት ረፈህ ከተማ በድሮን ሲደበደብ አድሯል።
- ሁለት መቶ የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰውተዋል በርካቶችም ቆስለዋል። አዎ ህጻናትና ሴቶች ይበዙበታል ብሏል አልጀዚራ።
- የሱሐይብ አል-ሂምስ የኩዌት ሆስፒታል ዳይሬክተር እንደገለፀው የወራሪዋ እስራኤል ጦር በረፈህ የተጠቀመችው ሚሳኤል በአለም አቀፍ ደረጃ የተከለከለና ሰውነትን የሚቆራርጥ ከጭንቅላት በላይ ጉዳት የሚያደርስ ነው።
- በረፈህ የሚገኘው ሆስፒታላችን ከሰዓታት በፊት በደረሰው ከባድ ጥቃት የተጎዱትን ሰዎች ለማስተናገድ ከአቅሙ በላይ ሆኗል።
- አምቡላንሶችና የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ከቤቶች ፍርስራሽ ስር የሞቱ ሰዎችን ጀናዛ ለማውጣት አሁንም እየሰሩ ነው ብሏል።
4 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group