Translation is not possible.

⭕️ቀሳሞች ለስምምነቱ ያቀረቡት ቅድመ ሁኔታ

🔹 ስምምነቱ ሶስት እርከኖች ሲኖሩት

እያንዳንዱ ደረጃ ለ45 ቀናት የሚቆይ እስረኞችን መለዋወጥ ወታደራዊ ከበባውን ማስቆምና ጋዛን መልሶ መገንባትን ያካትታል።

የስምምነቱን የመጀመሪያ ምዕራፍ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ እርምጃዎችን የያዘ ዝርዝር አባሪን ቀሳሞች አያይዘው ልከዋል።

🔹እስረኞችን በተመለከተ

ሕፃናትና ሴቶችን፣ አዛውንቶችና ሕሙማን የወራሪዋ እስረኞች ይፈታሉ። በተያያዘም በወራሪዋ እስር ቤት የሚገኙ 1500 ቁጥር ያላቸው ወንድም እህቶቻችን ይለቀቃሉ። ከእነርሱም ውስጥ 500 ያህሉ የዕድሜ ልክ እስራትና ከፍተኛ የቅጣት ውሳኔ በወራሪዋ እስራኤል የተፈረደባቸው ናቸው።

🔹ሰብዓዊ ዕርዳታን የጫኑ መኪኖች

  በቀን 500 ሰብዓዊ እርዳታን የጫኑ መኪኖች ነዳጅን ጨምሮ ወደ ጋዛ ይገባሉ በተለይም ወደ ሰሜናዊው ክልል እንዲገቡ ይደረጋል።

🔹መጠለያ

በቀን 60,000 ጊዜያዊ መጠለያ ቤቶች፣ የመጀመርያው የስምምነት እርከን ከመጠናቀቁ በፊትም 200,000 ጠንካራና ለመኖር አመቺ የሆኑ ድንኳኖች ይገነባሉ።

🔹የተፈናቀሉትን መመለስ

የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ፣ በሰሜን እና በደቡብ ጋዛ የመንቀሳቀስ ነፃነትና ዋስትና ይሰጣል።

🔹ግንባታዎች

ቤቶችን፣ ኢኮኖሚያዊ ተቋማትን እና የህዝብ መገልገያዎችን መልሶ የመገንባቱ እቅድ ፀድቆ ትግበራው ቢበዛ በ 3 ዓመታት ውስጥ እንዲጠናቀቅ ይደረጋል።

🔹 የወራሪዋ እስራኤል ጦር ከጋዛ መውጣት

  ከመጀመርያው የስምምነት እርከን በፊት የጠላት ኃይሎች ከተማውን ለቀው በመውጣት መልሶ ግንባታው እንዲጀመር ይደነግጋል።

🔹አለም አቀፍ ዋስትናዎች

  ኳታር፣ ግብፅ፣ አሜሪካ፣ ቱርክ እና ሩሲያ ለስምምነቱ ተግባራዊነት ዋስትናና ታዛቢ እንዲሆኑ ይጠይቃል። እና ሌሎችንም ሰርፕራይዞች ይዟል።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group