Наган дахаан йохтахам.

ፈላህ መስጂድ ለምን?‼

ሰሞኑን በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ መካኒሳ ጀርመን አደባባይ አካባቢ በሚገኘው ፈላህ መስጂድ  ለረጅም አመት በማን አለብኝነት  መስጂዱን ሲዘውር የነበረው ፅንፈኛው ቡድን ረብሻ ለማስነሳት ከፍተኛ ድብቅ ዝግጅት ሲያረግ ከርሟል ። ይህ ፅንፈኛ ቡድን የመጅሊስ መዋቅርን ሙሉ ለሙሉ አልቀበልም በማለት መስጂዱ ቂርኣትም ሆነ ቋሚ የሙሀደራ ፕሮግራም የለውም። የአካበቢው ሙስሊም ማህበረሰብ ወደ መስጂድ ገብቶ እንዳይማር ካለፈው ስርአት ጋር በመተባበር ሲያሳስሩ ሲጠቁሙ ሲያሸማቁ ቆይተዋል።

በቅርቡ መጅሊስ ከተቀየር ወዲህ አቋማቸውን ባለመቀየር በተደጋጋሚ ቢመከሩ አሻፈረኝ አንሰማም በማለት የመስጂዱን ንብረት እየተከፋፈሉ ፣ እየበዘበዙ ከርመዋል። ታዲያ የአካባቢው ማህበረሰብ በቃኝ ብሎ ደርስ ለመጀመር ደፋ ቀና ብሎ ሰሞኑን ቂርኣት የጀመረ ቢሆንም። ይህ ፅንፈኛ ቡድን ዛሬ ረብሻ አስነስቶ ብዙ ወንድሞች ተጎድተዋል።

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች  ማህበር

Send as a message
Share on my page
Share in the group