Translation is not possible.

በጨለማ ተጓዦችን… አበስራቸው‼

========================

✍ ምናልባትም ቀን ላይ ላብ ጠብ በሚያደርግ የጉልበት ሥራ ላይ አሳልፈህ ይሆናል፣ ናላን በሚያዞር የጭንቅላት ሥራ ተወጥረህ ይሆናል፣ በጠዋት የወጣህ ወደ ቤትህ የምትገባው አምሽተህ ይሆናል፣ ርቦህ ደክሞህ መጥተህ ትንሽ አረፍ እንዳልክ የፈጅር ሶላት ይደርስና በዙሪያህ ባሉ መስጂዶች «ሶላት ከእንቅልፍ በላጭ ነው፣ ኑ ወደ ሶላት፣ ኑ ፈላሕ ወደምትወጡበት መንገድ…» የሚል የጌታህን ጥሪ በአላህ ባሮች አንደበት ትሰማለህ።

ያኔ ነፍስህ በእንቅልፍ ሰመመን ውስጥ ሆና ከላይህ ላይ ያለውን ብርድልብስ አሽቀንጥረህ፣ ያንን ጣፋጭ እንቅልፍ ትተህ ለጌታህ ትዕዛዝ ምላሽ ለመስጠት ትነሳለህ ወይንስ «ቆይ ትንሽ እንቅልፌ ይውጣልኝና እነሳለሁ!» በሚል ሽንገላ ባልሰማ ጸጥ ብለህ ጸሐይ ሲወጣ መስገድ?  መቼም ከናካቴው አለመስገድ ይኖራል ብዬ አላስብም። አላህ ይጠብቀንና!

ፈጅር ላይ ከዚያ ደክሞህ ካገኘኸው ጣፋጭ እንቅልፍ ለመነሳት እነዚህ 3 ሐዲሦች በቂ ናቸውና ላስታውስህ ወደድኩ።

①ኛ) ለአንተ ገና ሳያዩህ በትካዜ የናፈቁህና  ሁሌም የሚቆረቆሩልህ አዛኙ ነቢይ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

(بشرِّ المشائينَ في الظلمِ إلى المساجدِ، بالنورِ التامِّ يومَ القيامةِ)

«በጨለማ ወደ መስጂድ ተጓዦችን የውመ-ል-ቂያማህ በሙሉ ኑር (ብርሃን) አበስራቸው።»

[ጃሚዑ-ስ'ሶጚር: 2129፣ ሶሒሕ አቡ ዳውድ: 561

Send as a message
Share on my page
Share in the group