Translation is not possible.

ልከክልህ እከክልኝ

ቁጥር አንድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

4፥82 *ቁርኣንን አያስተነትኑምን ከአላህ ሌላ ዘንድ በነበረ ኖሮ በእርሱ ውስጥ ብዙን መለያየት ባገኙ ነበር*፡፡ أَفَلَا يَتَدَبَّرُونَ الْقُرْآنَ ۚ وَلَوْ كَانَ مِنْ عِندِ غَيْرِ اللَّهِ لَوَجَدُوا فِيهِ اخْتِلَافًا كَثِيرًا

አንድን ሰው፦ "ያምሃልን? ስትሉት እርሱም፦ "አንተም ያምሃል" ካለ መታመሙን አረጋግጧል ማለት ነው። አንድን ሚሽነሪይ፦ "ባይብል ይጋጫል" ስትሉት እርሱም፦ "ቁርኣንም ይጋጫል" ካለ ባይብል መጋጨቱን አረጋግጧል ማለት ነው። ይህ እከክልኝ ልከክልህ ነገር ነው። አንድ ሚሽነሪይ፦ "ቁርኣን ይጋጫል" ቢለን እኛ፦ "እረ በፍጹም" እስቲ ጥቀሰው እንጂ ባይብልም ይጋጫል አንለውም። ምክንያቱም ባይብል የሰው ንግግር ስለገባበት እና ሥረ-መሠረቱ ሳይኖር ቀርቶ ቅጂ ስለሆነ፥ ገልባጮቹ ስህተት እንደሰሩ የባይብል ለዘብተኛም ጽንፈኛም ምሁራን ይስማማሉ። የቁርኣን ግጭት ተብሎ የቀረበው የዛሬ ስድስት ዓመት አንሰሪንግ ኢሥላም ላይ የቀረቡ እንጂ አዲስ ነገር የለውም። መልሱን በተከታታይ ኢንሻላህ በጽሑፍ እና በድምጽ እንሰጣለን፦

ጥያቄ 1

አጋሪ ሴቶችን ማግባት ተፈቅዷል ወይስ አልተፈቀደም?

አልተፈቀደም:-

ሱራ 2፡221 “በአላህ አጋሪ የሆኑ ሴቶችን እስኪያምኑ ድረስ አታግቧቸው፡፡

ተፈቅዷል:-

ሱራ 5፡5 “ከነዚያ ከናንተ በፊት መጽሐፍን ከተሰጡት ሴቶች ጥብቆቹም ዘማዊዎችና የሚስጢር ወዳጅ ያዢዎች ሳትሆኑ ጥብቆች ሆናችሁ መህሮቻቸውን በሰጣችኋቸው ጊዜ ልታገቧቸው የተፈቀዱ ናቸው።

Send as a message
Share on my page
Share in the group