Translation is not possible.

የቱርክ ፓርላማ እስራኤልን ይደግፋል በሚል ኮካ ኮላን አገደ!

...

(ሀሩን ሚዲያ፦ጥቅምት 27/2016)

...

የቱርክ የህዝብ እንደራሴዎሽ ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ እስራኤልን የሚደግፉ ኩባንያዎች ምርቶች በፓርላማ ግቢ ውስጥ በሚገኙ ሬስቶራንቶች፣ ካፍቴሪያዎች እና ሻይ ቤቶች እንዳይሸጡ ወስኗል።

..

የፓርላማው አፈ-ጉባዔ ኑማን ኩርቱልሙስ ውሳኔውን ያሳለፉ ሲሆን በመግለጫው ላይ ግን የኩባንያዎቹን ማንነት አልገለፁም። አንድ ምንጭ ለሮይተርስ የዜና ወኪል እንደገለጸው የኮካ ኮላ መጠጦች እና የኔስትል ፈጣን ቡና የተወገዱት የምርት ስሞች ሲሆኑ ውሳኔው በሕዝብ ፍላጎት የመጣ ነው ብለዋል።

..

በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አክቲቪስቶች የእስራኤልን እቃዎች እና በጋዛ ላይ የምታደርገውን ጥቃት የሚደግፉ ምዕራባውያን ኩባንያዎችን እንዲከለክል ጥሪ ሲያቀርቡ ቆይተዋል።

...

©ሀሩን ሚዲያ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group