Translation is not possible.

240 ነፍስ Vs 2.4 ሚሊዮን ነፍስ‼

========================

✍ የምዕራቡ ዓለምና ከፊል የአውሮፓው ዓለም ወራሪዋን ከጀርባ በሎጂስቲክስ እየደገፈ፤ በሐማስ ታስረውብኛል ያለቻቸውን 240 ሰዎች ለማስለቀቅ 2.4 ሚሊዮን ህዝብ በከበባ እስር ቤት ውስጥ አድርጋ እስካሁን ከ10 ሺህ በላይ የሚሆኑትን ገድላለች። ከነዚህ መካከል ከ4,100 በላይ የሚሆኑት ጨቅላ ህፃናት ናቸው። ከ2, 600 በላይ ሴቶች ተገድለዋል፣ 26,000 ገደማ ቁስለኞች ሆነዋል። በተለይ ከትናንት ጀምሮ ሆስፒታሎች የጥቃቱ ሰለባ ሆነዋል።

56 መስጂዶች ሙሉ በሙሉ ወድመዋል፣ 136 የሚሆኑት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል፣ ተጨማሪ 3 ቤተ ክርስቲያናት ወድመዋል።

40 ሺህ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ሲወድሙ ከ222 ሺህ በላይ የሚሆኑ ከፍተኛ ውድመት ደርሶባቸዋል።

47 ጋዜጠኞች፣ 53 የመስጂድ ኢማሞችና ዳዒዎች ተገድለዋል።

ይህ ሁሉ የሆነው የታገቱ 240 ሰዎችን ለማስለቀቅ ነው ተብሎ ጀስቲፋይ እየተደረገ ነው።

የታገቱትን ያለ ውጊያ በድርድር እንሰጣለን እየተባለ ባልሰማ ጭፍጨፋውን መቀጠሏ፤ ጋዛ ወደተለመደው በወረራ ወደያዘቻቸው ግዛቶቿ አጠቃላ ከቻለች ነዋሪዎቿን ወደ ግብፅ የሲናይ በረሃ ማሰደድ፣ በመቀጠልም ዛሬውኑ የጀመረቻቸውን የዌስት ባንክ፣ ረምላህ፣ እየሩሳሌምና ሌሎች አካባቢዎች የሚገኙ ፈለስጢናዊያንን ሙሉ በሙሉ አስወጥታ ከወንዙ እስከ ባህሩ የነበረውን የቀድሞ የፈለስጢን ግዛት ማጠቃለል ነው ህልሟ። ይህን ካሳካች በኋላ ደግሞ ሌሎች የዓረብ ሃገራት ተረኞቹ ፈለስጢን መሆናቸው ላይቀር ይችላል።

ገና ከወዲሁ ተረባርበው ይህቺን ነቀርሳ ከመሃላቸው መንቀል ሲገባቸው፤ እነርሱ ግን የነቁና የገባቸው አይመስልም። አላህ ያንቃቸውና!

ጋዛዊያንን ማፈናቀል ካልቻለች ግን ቢያንስ እንደ ሌሎቹ ክፍሎች ጨቁናና ረግጣ ለማስተዳደር ትፈልጋለች።

እየሆነ ያለው ነገር ያሳዝናል። ደም ጠጪዎቹ እነ አሜሪካ የሟቾች ቁጥር ስንት ሲደርስ እንደሚረኩ እስካሁን አልታወቀም።

አላህ ሆይ! ካንተ ውጭ መጠጊያ የለንምና ደካማ ባሮችህን በጥበብህ እርዳቸው፤ በጠላቶቻቸው ላይ ድልን አቀዳጃቸው፤ የመከራና የጨለማ ሌሊቶቻቸውን ከዚህ በላይ አታርዝምባቸው፤ ለሞቱት ሸሂድነትን፣ ላሉት ድልንና ሰላምን ከሶብርና ጽናት ጋር ወፍቃቸው።🤲

منقول

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group