لا يمكن الترجمة

ለጋዛ ሰርጥ የኑክሌር ቦምብን እንደ አማራጭ?! …

የኔታንያሁ ጥምር መንግሥት አባል የሆነው የኦዝማ የሁዲ ፓርቲ ​ባልደረባው የኢየሩሳሌም ጉዳዮችና የቅርሶች ሚኒስትር አሚኻይ ኤሊያሁ፣ [ሐማስን ለማጥፋት] በጋዛ ሰርጥ የኑክሌር ቦምብ መጣል "አንዱ አማራጭ ነው" ማለቱ ተሰማ።

የቀኝ ጽንፈኛው ሚኒስትር አሚኻይ ኤልያሁ፣ ኮል ቤራማ ለተባለ የሀገሪቱ ራዲዮ ጣቢያ በሰጠው ቃለ ምልልስ፣ "ጋዛ ውስጥ ተዋጊ ያልኾነ አንድም ሰው የለም" ካለ በኋላ፣ ለሰርጡ ነዋሪዎች ሰብኣዊ እርዳታ ማቅረብ "ውድቀት ነው" ማለቱን የእስራኤሉ ጋዜጣ ሐሬትዝ ዘግቧል።

በአንተ ዕይታ '[በጋዛ] ተዋጊ ያልኾነ ሰው ከሌለ'፣ የጋዛ ሰርጥን በኑክሌር ቦምብ ማጥቃት አማራጭ ነውን? ተብሎ የተጠየቀው ሚኒስትሩ፣ "ያ አንዱ አማራጭ ነው" ሲል መልሷል።

ይህን የተናገረው ሚኒስትር፣ በነውጠኛው ኢታማር ቤን ግቪር የሚመራው የኦዝማ የሁዲ ፓርቲ አባል ነው።

በዚሁ ቃለ ምልልስ ሚኒስትሩ፣ "የጋዛ ሰርጥ ሰሜናዊ ክፍል የመኖር መብት የለውም" ማለቱን ታይምስ ኦፍ እስራኤል ጽፏል።

ይኸው ሚኒስትር በቃለ ምልልሱ ላይ፣ "የፍልስጥኤምን ወይም የሐማስን ሰንደቅ የሚያውለበልብ ማንኛውም ሰው ከምድረ ገጽ መወገድ አለበት" ማለቱንም ታይምስ ኦፍ እስራኤል ጠቅሷል።

የሚኒስትሩን ንግግር መነሻ በማድረግ የተጠየቁት የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ፣ የኤልያሁ አስተያየት "ከእውነታ የተፋታ ነው" ካሉ በኋላ፣ "እስራኤል እና የእስራኤል መከላከያ ኃይል (IDF)፣ ተዋጊ ያልኾኑ [ንፁኃን] ሰዎችን ላለመጉዳት በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት እየተንቀሳቀሱ ነው" ሲሉ [በሰብኣዊ ፍጡራን ላይ ከማላገጥ የሚቆጠር] ምላሽ ሰጥተዋል።

ኔታንያሁ፣ እስካሁን ወደ 4 ሺህ የሚጠጉ ሕጻናትን ጨምሮ፣ በድምሩ 10 ሺህ የሚገመቱ ንፁኃን "ፍልስጥኤማውያንን የገደልነው፣ ዓለም አቀፍ ሕግን ተከትለን ነው" እያሉን ነው።

በእስራኤል የፖለቲካ ባህል፣ እንዲህ ያለ ከረር ያለ ንግግር የሚናገሩ፣ ወይም ዘግናኝ ጭፍጨፋ የፈፀሙ ጽዮናዊያንን ለጊዜው ገለል የማድረግ የቆየ ልማድ አለ።

አሁን ግን፣ በኔታንያሁ ትዕዛዝ ላለፈው አንድ ወር በጋዛ እየተፈፀመ ያለው የዘር ማጥፋት ወንጀል (the Crime of Genocide) እንደ Normal ተቆጥሮ፣ በነባሩ ልማድ መሠረት፣ ይህን አስደንጋጭ ንግግር የተናገረው ሚኒስትርም ለጊዜው ከኔታንያሁ ካቢኔ ገለል ተደርጓል።

ከጥቂት ጊዜ በኋላ ይህ ሰው በእስራኤል ፖለቲካ ውስጥ ቁንጮ ኾኖ እንደሚመጣ መጠራጠር አይቻልም - የሳብራ እና ሻቲላ ንፁኃንን እንዳስጨፈጨፈው ኤሪያል ሻሮን።

በነገራችን ላይ ኤርያል ሻሮን በስትሮክ ተመትቶ 'ክሊኒካሊ' ከሞተ በኋላ፣ ነፍሱ ከስጋው የተላቀቀችው፣ ሰው ሊቀርበው በማይችልበት ደረጃ ለሰባት ዓመታት ከተግማማ በኋላ ነው።

image
image
أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة