ترجمہ ممکن نہیں

የአልቃሳም ብርጌዶች ቃል አቀባይ አቡ ዑበይዳ ከተናገሩት ዋና ዋና ነገሮች፡-

⭕️ ሙጃሂዶቻችን በአስር ግንባሮች ከጽዮናውያን ጦር ጋር እየተፋለሙ ይገኛል።

⭕️ ታንኮችን አውድመናል የጦር መሪዎችን ማርከናል የበዙ የጠላት ወታደሮችን ገድለናል አቁስለናልም።

⭕️ ከጠላት ኋላ ተነስተን ከመከላከል ወደ ማጥቃት ተሸጋግረናል።

⭕️ ዛሬ ማምሻውን ከጋዛ ከተማ በስተሰሜንና በስተምዕራብ በኩል የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ ከፍተን 6 ታንኮችንና ሁለት የሰው ኃይል አጓጓዥ መኪናዎችን አውድመናል።

⭕️ የሟቾች ቁጥር የጽዮናዊያኑ ሚዲያ ከጠቀሰው እጅግ የላቀ ነው።

⭕️ "ነብር" የተሰኘውን የጠላት የሰው ኃይል ተሸካሚ ጦር ለማውደም በሚሳኤሎቻችን ባደረግነው የመጀመሪያ ሙከራ ዶግ አመድ ማድረግ ችለናል።

⭕️ በርካታ ወታደሮቻችሁ በጥቁር ከረጢት ተሸፍነው ሲመለሱ ጋዛን በጽዮናዊያኑ ላይ የታሪክ እርግማን እናደርግባቸዋለን የሚለው ንግግራችንን በሚገባ ታስታውሱታላችሁ።

⭕️ በሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችንን በሞት ማጣታችንና በሰማዕትነት መገደላቸው ህመማችንን ዋጥ አድርገን ለከባድ መስዋዕትነት እንድንዘጋጅ ጉልበት ሆኖናል copy

Send as a message
Share on my page
Share in the group