Translation is not possible.

ይልቅ የመርህ ሰው ሁን

~

ኢስላም መርህ ላይ የቆመ ሃይማኖት ነው። ስትጣላ "አሕ ^ ባሽ የሁ -ዲ ነው" እያሉ ጥግ የደረሰ ክስ መክሰስ፣ ስትታረቅ "አላህ ሙስሊም ብሎ ከጠራን በኋላ ለምን ትለያዩናላችሁ?" እያሉ ተኝቶ ማስተኛት ተቅዋ የተላበሰ አካሄድ አይደለም። የንፋሱን አቅጣጫ እያየ የሚገለባበጠው ፖለቲከኛ ነው። የሃይማኖት ሰው ሂዳያ የሚመኝለት ህዝብ እንጂ የምርጫ ካርዱን የሚጠብቀው ጭፍን ደጋፊ አያሻውም። ስለሆነም አቋሙ ወጥና የማይነቃነቅ ነው መሆን ያለበት።

ስትጣላ ሺር.ክ የነበረ ነገር ስትታረቅ ተውሒድ አይሆንም። ትላንት ቢድዐ የነበረ ጉዳይ ዛሬ ሱና አይሆንም። በጥመ^ቱ ጠ-ላት የሆነ አንጃ ከብልሹ እምነቱ ሳይመለስ ወዳጅ የሚሆንበት ሳይንስ የለም። ዐብደላህ አልሀረሪ ላይ ያወገዝከው ጥፋት ሰይድ ቁጥብ ላይ ሲደርስ ፅድቅ አይሆንም። ዑመር "ኮምቦልቻ" ላይ ያወገዝከው አቋም ሰመሀር ተክሌ ላይ ሲደርስ ተራ አለመግባባት አይሆንም። የጥመት ቡላና ዳለቻ የለውም።

በየዋህነት የዘነጉትን ለማስታወስ እንጂ በቡድን ተሸብበው ለሚያስቡት አይደለም የማወራው። መንታ መለኪያ (double standard) የአስመሳዮች አይነተኛ ባህሪ ነው። አማኝ በመርህ የሚጓዝ፣ ስሜቱን ረግጦ ለእውነት የሚወግን ነው መሆን ያለበት። በተረፈ አሕ - ባሽ ተነካ ብሎ በህይወት ጭምር የሚዝት እያየሁ ነው። ለዲን መቆርቆራቸውን ያላግባብ የሚያውሉ መሳኪን ወገኖች ያሳዝናሉ። "ተሰለፉ" ሲባሉ የሚሰለፉ፣ "በቃ ተውት አሁን አንድ ሆነናል" ሲባሉ ቀኝ ኋላ የሚዞሩ፣ ባላወቁት የስብከት ድግምት በገዛ ህሊናቸው ላይ የማዘዝ ስልጣን የተነፈጉ ሚስኪኖች አያሳዝኑም? ከቀደምት ዓሊሞች ውስጥ አንዱ የሆነን የጥፋት ቁንጮ አስመልክተው "ለሱ አይደለም የማዝነው። የማዝነው ላጠመማቸው ነው" ነበር ያሉት። በተመሳሳይ በዲን ጉዳይ እንደ ጥቅማቸው ዥዋዥዌ በሚጫወቱ አካላት ብዙ ወገናችን መጎዳቱ ያሳዝናል። ሲያውቅ የሚያጠፋውማ መርጦ ነው የገባበት።  ግን ሰው እንዳይከፋው ተብሎ ምን ማድረግ ይቻላል?

=

የቴሌግራም ቻናል :-

t.me/IbnuMunewor

Send as a message
Share on my page
Share in the group