Translation is not possible.

🗯 <አላህ ዲንን አግርቶታል፣ ከዚህ ውጭ ሌላ የፈለገ እነሱ ናቸው ድንበር አላፊዎች>

©ሸይኽ ኢልያስ አህመድ

🔰 ብዙ ጊዜ ሰዎች በተለያዩ አጋጣሚዎች የሚተገብሯቸው በስፋት ብዙሀኑ ዘንድ የሚፈጸሙ ጉዳዮች በቀላል እይታ እንዲታዩ ምክንያት ይፈለጋል፣ ነገሮችን የማግራራት ሂደት ነው። ይህ እዚህ ደረጃ ከመድረሱ በፊት እንደመሸጋገሪያ የተወጣጣበት ደረጃዎች አሉት። እሱም ዲን ገር ነው የሚል ዐረፍተነገር ነው። ይቺህ ዐረፍተነገር ትክክለኛ ዐረፍተነገር ነች፣ ከሊመቱል ሀቂን፣ ግን ኡሪደ ቢሀል ባጢል፣ እውነተኛ አባባል ሆና ሳለ ከበስተኋላዋ የታጎረው እውነተኛ ያልሆነ አላማ ነው፣ ምንም እንኳን ይህንን ዐረፍተነገር በዚህ ሂደትና አገባብ ያነገበው ግለሰብ ወይም አንጃ በትክክል ውሸትን በውሸትነት ፈልጎ ላይሆን ቢችልም!

🔰 ሁላችንም ማወቅ የሚገባን ነገር ዲን ገር ነው ሲባል አላህ ዲንን ገር አድርጎ ደንግጎታል ማለት ነው። ዲን ገር ስለሆነ እኛ እናግራራው አይባልም። አላህ ያገራውን ዲን ይበልጥ ለመለጠጥ  ጥረት የሚያደርግ ካለ ለሱ የምንለው…

<አላህ ዲንን አግርቶታል፣

{فَمَنِ ٱبْتَغَىٰ وَرَآءَ ذَٰلِكَ فَأُو۟لَٰٓئِكَ هُمُ ٱلْعَادُونَ}

ከዚህ ውጭ ሌላ የፈለገ እነሱ ናቸው ድንበር አላፊዎች> እንደተባለው ነው።

🔰 ዲንን የሚያገራው አላህ ነው። ነዓም አላህ በደነገገው ዲን እና እሱ ባሰፈረው ህግ ላይ ራሱ በአንዳንድ ሁኔታዎች ላይ የተከለከሉ ነገሮች ሊፈቀዱ እንደሚችሉ አውቀናል።

{وَقَدْ فَصَّلَ لَكُم مَّا حَرَّمَ عَلَيْكُمْ إِلَّا مَا ٱضْطُرِرْتُمْ إِلَيْهِ} ፣

<<በእናንተ ላይ እርም ያደረገላችሁን ነገር በዝርዝር ጠቅሶላችኋል፣ እናንተ ተገዳችሁ የምትፈጽሙት ካልሆነ በስተቀር>>።

#ነገርግን ጥቅል ይዘቱ እንደታወቀ [ሀራም እንደሆነ] ይቀጥላል!

Send as a message
Share on my page
Share in the group