Tarjima qilib boʻlmadi.

ሥራ አጥቶ እየተንከራተተ ያለን "መቼ ነው ሥራ የምትጀምረው?" ብለህ ሌላ ጭንቀት አትጨምርበት።

አማራጭ ሲጠፋው ሀገሩን ለቆ በስደት ያለን "መቼ ነው የምትመለሰው?" እያልክ ብሶቱን አትቀስቅስበት።

ትዳር የዘገየባትን ሴት "መቼ ነው የምታገቢው?" እያልክ አትነዝንዛት። ራስ ምታት አትሁንባት!

ሀሳብና ጭንቀታቸውን ታግለው አፍነው የአላህን ፈረጅ በትዕግስት የሚጠባበቁን ጥያቄ በማብዛት ሌላ ችግር አትሁንባቸው።

ምን እንደሚጠብቁ አትጠይቃቸው!

ከመጠበቅ ውጪ ሌላ አማራጭ ቢኖራቸው ያደርጉት ነበር!!

ሪዝቅ ያለው በአንተ ሳይሆን በአላህ እጅ ነውና ተዋቸው። ከቻልክ አግዛቸው፤ አልያም ዱዓ አድርግላቸው! ካልቻልክ አትረብሻቸው ዝም በላቸው!

ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉ ለሌሎችም ሼር ያድርጉ!

👇

t.me/AbuMeryemNeja

Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish