✍️
ስለ አቅሷ ምን ያውቃሉ??
🕌አቅሷ ማለት፦
ነብዩﷺ ከጌታቸው ሰላት ለመቀበል ወደ ሰማይ ሲወጡ ጉዞ ያደረጉባት መስጂድ ናት።
{سُبْحَانَ الَّذِي أَسْرَى بِعَبْدِهِ لَيْلًا مِّنَ الْمَسْجِدِ الْحَرَامِ إِلَى الْمَسْجِدِ الْأَقْصَى الَّذِي بَارَكْنَا حَوْلَهُ لِنُرِيَهُ مِنْ آيَاتِنَا إِنَّهُ هُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ}
{ያ ባሪያውን ከተከበረው መስጂድ ወደዚያ ዙሪያውን ወደ ባረክነው ወደ አቅሷ መስጂድ በሌሊት ውስጥ ያስኼደው (ጌታ) ጥራት ይገባው። ከተዓምራቶቻችን ልናሳየው (አስኼድነው)፡፡ እነሆ እርሱ ሰሚው ተመልካቺው ነው፡፡}
[አል_ኢስራእ:1]
🕌አቅሷ ማለት፦
ሙስሊሞች ከሂጅራ በኋላ ለአስራ ሰባት ወራት አካባቢ ተቀጣጭተው የሰገዱባት የመጀመሪያዋ ቂብላ ናት።
🕌አቅሷ ማለት፦
መካ ከምትገኘው መስጂደል ሓራም እና መዲና ከምትገኘው መስጂደል ነበዊ ቀጥሎ ጓዝ ጠቅልሎ መሄድ የተደነገገላት ሶስተኛዋ መስጂድ ናት።
🕌አቅሷ ማለት፦
ነብዩﷺ ኢስራእ ባረጉበት ሌሊት ሁሉም ነብያቶች ተሰብስበውላቸው ኢማም ሆነው ያሰገዱባት መስጂድ ናት።
🕌አቅሷ ማለት፦
መስጂደል ሓራም እና መስጂደል ነበዊ ሲቀር ሌላ ቦታ ከሚሰገድ ሰላት እሷ ላይ ሲሰገድ አምስት መቶ እጥፍ በላጭነት ያለው መስጂድ ናት።
🕌አቅሷ ማለት፦
ከመስጂደል ሓራም ቀጥሎ ምድር ላይ የተገነባችው ሁለተኛዋ መስጂድ ናት።
🕌አቅሷ ማለት፦
አላህ እሷንም ዙሪያዋንም በረካ ያደረጋት የሆነች መስጂድ ናት። {…الَّذِي بَارَكْنَا حَوْلَهُ…}
🕌አቅሳ ማለት፦
ነብዩላህ ሙሳﷺ አላህ ወደ እሷ አስጠግቶ እንዲያሞተው እና እዝያው አካባቢ እንዲቀበር የተማፀነው ቦታ ናት።
🕌አቅሷ ማለት
ቡኻሪ በዘገበው ነብዩﷺ እንዲህ ይላሉ፦
«ነብዩ ሱለይማን መስጂደል አቅሷ ገንብቶ ካጠናቀቀ በኋላ ለአላህ ሶስት ነገር እንዲሰጠው ለመነው። "ፍርዱ የአላህን ፍርድ እንዲገጥም፣ ለማንም ሰው የማይሰጥ የሆነ ንግስና እንዲሰጠው እና ማንኛውም ሰው ሰላትን ለመስገድ ብቻ ፈልጎ ወደዚህ መስጂድ የመጣ እንደሆነ ከመስጂዱ ሲወጣ እናቱ እንደ ወለደችው ቀን ከወንጀሉ የነፃ ሆኖ እንዲወጣ" ነብዩﷺ ሁለቱ እንኳ በእርግጥም ተሰጥቶታል፤ ሶስተኛውም እንደ ተሰጠው እከጅላለሁ» ብለዋል።
🕌አቅሷ ማለት፦
የቂያማ ቀን መቀሽቀሻዋ ምድር ናት። መይሙና ቢንት ሳዕድ አስተላልፋው ኢማሙ አልባኒ ሰኺኽ ብለውታል።
🕌አቅሷ ማለት፦
የሚያረጋግጥ ግልፅ መረጃ ባይገኝም: ለመጀመሪያ ጊዜ የገነባው ከፊሎች አባታችን ኣደም፣ ከፊሎቹ የነብዩ ኑሕ ልጅ፣ ሌሎቹ ደግሞ ነብዩ ኢብራሂም እንደ ገነቧት ይዘግባሉ። ከዝያም ነብዩላህ ሱለይማን አሳምረው እንደገነቧት ታሪክ ዘጋቢዎች ያወሳሉ።
ይህም የመስጂዷ ትልቅነት ከሚያሳዩ ነጥቦች አንዱ ነው።
ዓለም የካዳት ሙስሊሞች የረሷት አቅሷ እነሆ ዛሬ ውሻ ሆኖ ከመኖር አንበሳ ሆኖ መሞት ምርጫቸው ያደረጉ ጀግና ልጆቿ "ለበይኪ ለበይኪ ያ አቅሷ" ብለው ተነስተዋል።
አላህ የድል ባንዲራ ያስጨብጣቸው!!
ለበይኪ ለበይኪ ለበይኪ ያ አቅሷ
{وَأُخْرَى تُحِبُّونَهَا نَصْرٌ مِّنَ اللَّهِ وَفَتْحٌ قَرِيبٌ وَبَشِّرِ الْمُؤْمِنِينَ}
አብሽሩ ኢንሻ አላህ ድሉ ቅርብ ነው!!
Komentar telah berhasil dilaporkan
Postingan telah berhasil ditambahkan ke linimasa Anda!
Anda telah mencapai batas teman 100000 Anda!
Kesalahan ukuran file: File melebihi batas yang diizinkan (9 GB) dan tidak dapat diunggah.
Video Anda sedang diproses, kami akan memberi tahu Anda ketika sudah siap untuk ditonton.
Tidak mungkin untuk mengunggah file tersebut: Jenis file ini tidak didukung.
Kami telah mendeteksi konten dewasa pada gambar yang diunggah, oleh karena itu kami menolak proses pengunggahan.
Untuk mendapatkan verifikasi (tanda centang) di jaringan sosial Islam Umma Life, Anda harus memenuhi salah satu dari kriteria berikut: 1. Aktifitas di jaringan sosial: Anggota yang berusaha untuk diverifikasi harus menjadi pengguna aktif di jaringan sosial. Anda harus memposting setidaknya satu pesan bermanfaat per hari, dan topik pesan tidak hanya berhubungan dengan agama. 2. Blogger Islam atau Muslim terkenal: Jika Anda adalah seorang blogger Islam atau Muslim terkenal, bahkan jika aktivitas Anda tidak berkaitan dengan topik agama di internet, Anda juga dapat bersaing untuk verifikasi. 3. Jumlah pelanggan atau pengelolaan halaman agama aktif: Jika Anda memiliki banyak pelanggan di jaringan sosial atau secara aktif mengelola halaman agama yang bermanfaat, ini juga dapat menjadi dasar untuk mendapatkan verifikasi