Çeviri imkansız.

ይህ ተሞክሮ ጥሩ ሳይሆን አይቅርም😝

የአፄው መሪዎች በከፍተኛው ማኅበረሰብ ዘንድ ጋብቻ ፖለቲካዊ አጋርነት ወይም ኅብረትን መፍጠሪያ ዋነኛ ማሣሪያም ነበር ለማለት ይቻላል።በተለይ ቀኃሥ (ጃንሆይ) በዚህ መሣሪያ በሚገባ ተጠቅመውበታል። ሀሳቡን የበለጠ ተጨባጭ ለማድረግ እንዲያግዘን ጥቂት አስረጅዎችን ወስደን እንመለከት።

ጃንሆይ አልጋ ወራሻቸው ልዑል አስፋወሰንን በመጀመሪያ ያጋቡት ከትግራዩ መስፍን ከልዑል ራስ ሥዩም ልጅ ከልዕልት ወለተእስራኤል ጋር ነበር። ልዕልት ዘነበወርቅ በመባል የሚታወቁት ሴት ልጃቸውን የዳሩት ለትግራይ ባላባት ለደጃዝማች ኃይለሥላሴ ጉግሳ ነበር። ልዕልት ተናኘወርቅ የተባሉት ልጃቸውን የዳሩት ደግሞ ለጉራጌው ባላባት ለራስ ደስታ ዳምጠው ነበር። ልዑል መኮንን የተጋቡት ከትግራይ ባላባት ልጅ ከልዕልት ሳራ ግዛው በተማሪዎች ትግል ውስጥ ዝነኛ የነበረው የጥላሁን ግዛው እህት ሲሆን የመጨረሻ ልጃቸው ልዑል ሣህለሥላሴ የሚባሉት ደግሞ የተጋቡት ከወለጋው ንጉሥ ከደጃዝማች ገበረእግዚአብሔር የልጅ ልጅ ከልዕልት ማኅፀንተ ጋር ነበር።

የቀኃሥ የልጅ ልጆቻቸውም ጋብቻ እንዲሁ ከፖለቲካ አንፃር እየታየ የተካሄደ ነበር። በዚህ መሠረት የአልጋ ወራሽ የመጀመሪያ ልጅ ልዕልት እጅጋየሁ የተዳሩት ለወለጋው ንጉሥ የልጅ ልጅ ለደጃዝማች ፍቅረሥላሴ ነበር። በዚህ አንፃር በርካታ ልጆችን የወለዱት ልዕልት ተናኘወርቅ አስተዋጽኦ በጣም ከፍተኛ ነበር። ልዕልት አይዳ የሚባሉት ልጃቸው የተዳሩት ለስመጥሩ የትግራይ መስፍን ለልዑል ራስ መንገሻ ሥዩም፣ ልዕልት ሰብለ ደስታ ለወለጋው ንጉሥ (ጆቴ) የልጅ ልጅ በጣም ተወዳጅ ለነበሩት ለደጃዝማች ካሣ ወልደማርያም፣ እመቤት ሜሪ አበበ ለኤርትራያዊው አቶ ሥዩም ሐረጎት ሲሆን ልዕልት ሂሩት የሚባሉት ለጎንደሬው ሌ ጀኔራል ነጋ ተግኝ ነበር የተዳሩት። የልዕልት ተናኘወቅ ወንድ ልጅ የባሕር ኃይሉ አዛዥ ኮሞዶር እስከንድር ደስታ ደግሞ በጃንሆይ ካቢኔ ሚኒስትር የነበሩትን የአቶ አማኑኤል ይህም የሚያመለከተው ከሀገር ግንባታ አንፃር ንጉሠ ነገሥቱ ከፍተኛ ትኩረት የሰጡት በዋናነት ከተለያዩ ብሔረሰቦች መሳፍንትና ባላባቶች ጋር የነበረውን ኅብረትንና ቁርኝት ለማጠናከር መሆኑ ነው። የተካሄዱት ጋብቻዎች ከሁሉም ወገን ከከፍተኛው ማኅበራዊ ክፍሎች ጋር ቢሆንም አላማው የተለያዩ ብሔረሰቦች ሕዝቦች በሀገሪቱ ፖለቲካ ሕይወት ውስጥ ያለተቃውሞ እንዲገዙ በአማች ፖለቲካ ጠፍሮ መያዝ ነው።

እና ብሄር ብሄረሰቦች የጥንቱን ለማስቀጣል ከእየብሄሩ ብናገባ ባይ ነኝ😝

አቶ ስዩም ሐረጎት ግን እመቤት ሜሪን የመሰሉ ቆንጆ አግብተው አሰብ የኤርትራ ነው ሊሉ ነው? እንኳ አሰብ አስመራም የእኛ ነው። እዚህ አዲስአበባ ላይ ኤርትራዊያንን ያገባችሁ x ብሄሮች ውልዱ ክበዱ።

ከአዱኛ ሙጬ

Mesaj olarak gönder
Sayfamda paylaş
Grupta paylaş