Translation is not possible.

ኢትዮጵያ ጦሯን በሁለት አቅጣጫ ወደ ኤርትራ ድንበር እያስጠጋች እንደሆነ በአለምአቀፍ ሚዲያዎች እየተዘገበ ይገኛል፡፡

1. አንደኛው ከመቀሌ የተንቀሳቀሰ ጦር አዲግራትን ተሻግሮ ወደ ጾረና ግንባር የተጠጋ ሲሆን፤

2. ሁለተኛው ደግሞ ከመሐል ሐገር በመንቀሳቀስ ወደ አሰብ አቅጣጫ ቡሬ ግንባር ነው፡፡

የሁለቱም የዚህ ሳምንት የሰራዊት እንቅስቃሴ አሰብ ግዛትን በመቁረጥ ለመቆጣጠር ሳይሆን አልቀረም፡፡ በዚህ ሂደት ትግራይ ክልልም ዛላምበሳ፤ ራማ፤ ባድመን እና ሌሎች በኤርትራ ስር በወረራ ተይዘው የሚገኙትን ግዛቶቿን ከሻብያ ለማስመለስ የተጣደፈች ይመስላል፡፡ ካርታውን ከታች ተመልከቱ፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚህ ሳምንት ኢትዮጵያ ከሻብያ ጋር ለምታደርገው የትኛውም ግጭት ህጋዊ መሰረት ለመጣል፤ ለተባበሩት መንግስታት እና ለምእራባዊያን እንዲሁም ለወዳጆቿ፤ ኤርትራን በወረራ እና የኢትዮጵያን የውስጥ ሰላም ጣልቃ እየገባ እንደሚበጠብጥ በመክሰስ ደብዳቤ ልካለች፡፡ ደብዳቤው የሚለው ባጭሩ፡-

ኢትዮጵያ ከትግራይ ክልል ጋር በደረሰችው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት፤ ስምንቱን ለመተግበር መንግስት እና የትግራይ ክልል በሚጥሩበት ግዜ የኤርትራ መንግስት ስምምነቱ እንዳይተገበር የሰላም ውሉን እያደናቀፈች ትገኛለች ብሏል፡፡ እንዲሁም የትግራይን የተወሰነ ክፍል በጉልበት መያዟን እንደቀጠለች እና በአማራ ክልል የሚገኙ የፋኖ ታጣቂዎችን በመርዳት ሐገር እየረበሸች ነው ሲል ለምዕራባውያን ሀገራት ደብዳቤ ልኳል።

በአንጻሩ የኤርትራ መንግስት ምእራባዊያንን የምትሰድብ፤ የተባበሩት መንግስታትን (UNን) ሁሌ የምታጣጥል ሐገር ስትሆን፤ በቅርቡ ዩክሬን ስተወረር ለራሻ በማገዝ ወደ ጦርነት አስገቡን እስከማለት የደረሰ እና አለም እንዲሁም የአፍሪካ መሪዎች ያወገዙት እና ያፈሩበት ነው፡፡ ሰውዬው በዚህ እድሜው ጦርነት ናፋቂ መሆኑን ሁሉም በአግራሞት የተመለከተበት አጋጣሚ ነበር፡፡

ስለዚህ የሻብያ መንግስት በጉልበት የያዛቸውን የትግራይ መሬቶችን እና የኢትዮጵያ የባህርዳርቻዎችን በራሱ ጉልበት ከኢትዮጵያ እና ከትግራይ ጋር በየትኛውም ግጭት ተጋፍጦ ለመከላከል የሚጥር እና የሚመጣውን ሽንፈት በግሉ ለመቀበል የተዘጋጀ ይመስላል፡፡ ሻብያ የምእራቡ አለም ጋር ሆድና ጀርባ ሲሆን የሚተማመነው የግብጽን እርዳታ ብቻ ነው!

"Eyewitnesses report the ENDF transported vehicles, some carrying heavy weapons, from Mekelle towards Tsorena. Eyewitnesses also say there are military activities from Adigrat onwards bordering Eritrea to Zalambessa"

"It has also been heard that the Eritrean army has increased its deployment of troops, including in Ethiopian territories it controls. Military movement in areas of the Afar region bordering Eritrea have also been reported to have continued"

Ethiopia sent a letter this week to western countries, stating that Eritrea is obstructing the Cessation of Hostilities Agreement, continues to occupy parts of Tigray and is arming the Fano militia in Amhara region.

Send as a message
Share on my page
Share in the group