Translation is not possible.

በፍልስጤሟ ምድር ጋዛ ወራሪዋ ከሰማይ በወረወረችው የድሮን እሳት ቤታቸው ዶግ አመድ ሆኖ በላያቸው ላይ ተናደ። አስራ አንድ ሙሉ ቤተሰብ ከፍርስራሹ መሐል ተጋደመ። በቦታው የደረሱት የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ቆፍረውና ቧጠው ሲያወጧቸው ሁሉም ሞተው እናት ነፍሷ ከጀሰዷ ሊላቀቅ የመጨረሻ እስትንፋሷ ላይ ነበረች።

በዝግታ አይኗን እያስለመለመች ታቃስታለች። በሆዷ የታቀፈችው ፅንስ በህይወት ይቆይ ዘንድ እግሯን ከፈት ልጇን ደገፍ አድርጋ ተንጋላለች። ሆስፒታል እንደደረሰች እስትንፋሷ ተቋርጦ ጌታዋን ስትገናኝ ፅንሱ ግን በህይወት ነበር። ዶክተሮች በአላህ ፈቃድ የልጁን ህይወት ማትረፍ ቻሉ። አስራ አንድ ሙሉ ቤተሰቦቹን ባጣበት ቅፅበት እርሱ ይህቺን አለም ተቀላቀለ። መገን የአላህዬ ነገር Mahi Mahisho

Send as a message
Share on my page
Share in the group