amemegfi2010 shared a
Translation is not possible.

Date: Oct 21, 2023

እንደብዙሃኞቹ የታሪክ ምሁራኖች ሀሳብ በአስረኛው የመልእክተኝነት አመት በአንዲት ሌሊት ሶስት ታላላቅ ተአምሮች ተከሰቱ። እነሱም የልብ ቀዶ ጥገና፣ ኢስራእ እና ሚዕራጅ ናቸው። የአቅሷው ጉዞ በኢስራእ ምእራፍ ሲጠቀስ የሰማዩ ጉዞ ደግሞ በነጅም ምእራፍ ላይ ተገልጿ

ጉዞው ከመጀመሩ በፊት ጂብሪል عليه والسلام ደረታቸውን ቀድዶ ልባቸው አውጥቶ፤ በዘምዘም ውሃ ካጠበውና ኢማንን ከጥበብ ጋር ቀላቅሎ ከጨመረበት በኋላ ወደ ቦታው መለሰው። ከዚያም ደረታቸውን ሰፋው። ይሄ ለሁለተኛው ጊዜ የተደገመ ተኣምር መሆኑ ነው

ከአህያ ከፍ ያለ እና ከበቅሎ ያነሰ፣ ከእይታው መጨረሻ ላይ የሚረገጥ፣ ነጭ አንፀባራቂ ( ቡራቅ ) መጓጓዣ ተመቻቸላቸውና በእሱ ከሀረም መስጅድ ወደ አቅሷ መስጅድ አቀኑ። ከዚህ በዘለለ የመጓጓዣው ምስልም ይሁን ምንነት አይታወቅም።

አቅሷ መስጅድ ሲገቡ ጌታችን ነብያቶችን عليهم الصلاة والسلام ሁሉ ሰብስቧቸው አገኙ። በነብያችን ኢማምነት ሁሉም ሁለት ረከዓ በጀመዓ ሰገዱ

ከሶላቱ በኋላ ከጂብሪል ጋር በመሆን ወደ ሰማይ ተጓዙ። የመሰላሉን ምንነት አላህ ብቻ ነው የሚያውቀው።

በቅደም ተከተል ከአንደኛው እስከ ሰባተኛው ሰማይ ከአደም፣ ዒሳና የህያ፣ ዩሱፍ፣ ኢድሪስ፣ ሀሩን፣ ሙሳ እና ኢብራሂም عليهم الصلاة والسلام ጋር ተዋወቁ።

በእለቱ ተቀጣጣይዋን እሳት እና ጠባቂዋን ማሊክን عليه السلام አይተዋል። የዝሙተኞችን፣ የወለድ ተጠቃሚዎችን፣ በእውቀታቸው የማይተገብሩ ሰዎችን እና የሀሜተኞችን ቅጣት ተመልክተዋል። በሌላ በኩል ደግሞ ጀነትን እና በውስጧ የሚገኙትን የዑመር ቢን ኸጧብን رضي الله عنها ህንፃ፣ የዘይድ ቢን ሀሪሳን رضي الله عنها ቆንጂት፣ ሁለት የጀነት ወንዞችን እንድሁም የናይልን እና የኤፍራጠስን ወንዞች ምንጭ ለማየት በቅተዋል።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group