Translation is not possible.

የእስራኤል ጦር የእዝ ሰንሰለቱ እየተበጣጠሰበት ይገኛል ። ይህም በመሆኑ የሎጀስቲክ እና የመሳሪያ አቅርቦቱ እየተቆራረጠ የእስራኤልን ጦር እንደፈለገ ማጥቃት እንዳይችል አስችሎታል !

ይህንን የእዝ መበጣጠስና የመሳሪያ እጥረት ለመፍታት እስራኤል ከላይ በአይሮፕላን የጦር መሳሪያ ለወታደሮቿ እያዘነበች ትገኛለች ። እስራኤል እንደዚህ አይነት ነገር ስታደርግ ከሂዝቡላህ ጦርነት በሗላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው !

እስራኤል እንደገለፀቺው ከሆነ እስካሁን 7 ቶን የጦር መሳሪያ ከአየር ላይ አውርዳለች ። ጦር መሳሪያው በፓራሹት ተደርጎ ወደምድር ይላክና መሬት ላይ ሲወድቅ ወታደሮቹ አንስተው እንዲጠቀሙት ነው ። እስራኤል ይህ ለማድረግ የተገደደቺው ጦሯ በሀማስ ጥቃት ለመንቀሳቀስና መሳሪያ ለማጓጓዝ ስለቸገረው ነው ። በርካታ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎቿ በሀማስ የወደሙባት እስራኤል በአየር መጣልን አማራጭ አድርጋዋለች ።

በሌላ በኩል ዛሬ ሀማስ በእስራኤል ጦር ላይ በከፈተው ከፍተኛ የመልሶ ማጥቃት የእስራኤል ጦር ከአልቀሳኢብ ሸሽቶ ወጥቷል ። የእስራኤል ጦር ወደሗላ ሲያፈገፍግም ሀማስ መሳሪያዎችንና መረጃዎችን ማግኘት ችሏል ።

እስራኤል ዛሬ እንደገለፀቺው ሀማስ በፈፀመው ወጥመዳዊ ጥቃት ሰባት ወታደሮቿን ማጣቷን ገልፃለች ። እስራኤል የምትጠቅሰው ቁጥር ከእውነተኛው ቁጥር በጣም ያነሰ መሆኑን ልብ ይሏል !!!

እስራኤል ወደ ጋዛ ስትገባ ሀማስ የምድር ውስጥ ዋሻዎቱ ውስጥ ተሸሽጎ የሚዋጋት መስሏት ነበረ ። እናም የዋሻ ውጊያ ለማድረግ አቅዳ ነበር የሄደቺው ። ግና የጠበቃት ሌላ ነው !

ሀማስ በዋሻ እየተሹለከለከ የሚዋጋ ሳይሆን ፊት ለፊት እየጠበቀ ወታደራዊ ኢላማዎቿን እያደባየ የሚዋጋ ትልቅ አቅምና የመዋጋት ሞራልን የታጠቀ መሆኑ እስራኤልን ብቻ ሳይሆን አባቷን አሜሪካን ጭምር አስደንግጧል ። ለዚህም አሜሪካ እስራኤልን እስከ መጪው ጥር ወር ድረስ የግደታ ጦርነቱን ማጠናቀቀ አለብሽ የሚል ግዴታን በእስራኤል ላይ መጣሏን New york times ያወጣው መረጃ ያሳያል።

እስራኤል እንኳንስ የዋሻ ውስጥ ውጊያ ልታካሒድ ይቅርና ዋሻዎቹን መቅረብ ራሱ ፈርታለች ። እስራኤል ዋሻዎቹን ለመቅረብ የሞከረቺው ሁለት ጊዜ ብቻ ነው ። አንዴ በወታደራዊ መሀንድሶችና በምሽግ ቴክኒሺያኖች ጭምር የታገዘ ወደ ዋሻዎቹ የመግባት ሙከራ አድርጋ ውጤቱም ለመግባት የሞከሩት ወታደሮቿ በቅፅበት ማለቃቸው ሆኗል ። ለሁለተኛ ጊዜ ታጋች ወታደሮቿን ለማስለቀቅ በሚል ያደረገቺው የመግባት ሙከራም ሰባቱን ወታደሮቿን ጨምሮ ታጋች ወታደሮቿን ካስጨረሰባት በሗላ ዳግመኛ ለመሞከር የነበራት ሞራል ተንከሽክሾ ፍርሀትን ለቆባታል ።

እናም ያላት አማራጭ ከሰማይ ቦንቦችን ማዝነብ ነው ። ግና ይህ የፍልስጤም ህፃናትን ይጨረስ እንደሆን እንጅ አሸናፊያ ሊያደርጋት እንደማይችል እሙን ነው ።

አረቦች እስራኤልን ይፈራሉ እስራኤል ደግሞ ሀማስን ትፈራለች !!

ድልም የሙጃሂዶች ይሆናይሆናል!

Send as a message
Share on my page
Share in the group